Job Expired
Minaye PLC
Business
Human Resource Management
Addis Ababa
3 years - 4 years
1 Position
2024-06-26
to
2024-06-28
Public Administration
TVET
Management
Full Time
Share
Job Description
ክፍሉን ሥራ ማቀድና ማደራጀት፣ ማስተባበር፣ መምራትና መቆጣጠር፣ የድርጅቱን የሰው ኃይል ቅጥር፣ ዕድገት፣ ዝውውር እንዲሁም ስንብት ፎርማሊቲን ማከናወን፣ በሠራተኞች ዘንድ የሥራ ዲሲፕሊን እንዲከበር ማድረግ፣ የመብራት፣ የውኃ፣ የስልክ፣ የትራንስፖርትና የጥበቃ፣ የጽዳትና የመላላክ የፎቶ ኮፒ አገልግሎት የተሟሉ መሆናቸውን መከታተልና መቆጣጠር፣ የድርጅቱን መኪናዎች ለስራ ማሰማራትናመቆጣጠር፣ የመኪኖቹን ደህንነት ማረጋገጥ፣ልዩ ልዩ የሥራ ልብሶች በወቅቱ ለሠራተኛው መድረሳቸውን ማረጋገጥ የጠቅላላ አገልግሎት ሥራዎች የሚቀላጠፉበትንና የሚሻሻሉበትን መንገድ በማጥናት ማቅረብና ሲፈቀድ ሥራ ላይ ማዋል።
የስራ ቦታ :-ቃሊቲ
የዋና ክፍሉን ሥራ ያቅዳል፣ ያደራጃል፣ በሥሩ ያሉትን ሠራተኞች ይመራል፣ ያስተባብራል፣ ይቆጣጠራል፤
በድርጅቱ የአስተዳደር ህጎች፣ ደንቦችና መመሪያዎች መሠረት የድርጅቱን የሰው ሀይል ያስተዳድራል፣ ቀልጣፋ የአስተዳደር ሥርዓት እንዲዘረጋ ያደርጋል፤
በተለያዩ ምክንያት ድርጅቱን በሚለቁ ሠራተኞች ምትክ ተገቢው የሰው ኃይል እንዲተካ ለሚመለከታቸው የዘርፍ ሃላፊዎች ያሳውቃል፣ለቅጥሩም ቅድመ ዝግጅት ያደርጋል፤
ለድርጅቱ ልዩ ልዩ አገልግሎት የሚውሉትን የውኃ፣ የመብራት፣ የስልክ፣ የነዳጅ፣ የትራንሰፖርት፣ እንዲሁም ኢንሹራንስ፣ ለመዝናኛ ክበብ አገልግሎት የሚውሉ ዕቃዎች መሟላታቸውን ይከታተላል፣ ይቆጣጠራል፣ ያልተሟሉ መገልገያዎችና ዕቃዎች ካሉ እንዲሟሉ ዝርዝር ሪፖርት ለቅርብ አለቃው ያቀርባል፣ አፈፃፀሙንም ይከታተላል፤
የጠቅላላ አገልግሎት ሥራ በተሻለ ቅልጥፍናና ጥራት ስለሚሰጥበት ሁኔታ ጥናት በማድረግ ለሃላፊው አቅርቦ ያስወስናል፣ ሲፈቀድም ሥራ ላይ መዋሉን ይቆጣጠራል፤ ለክፍሉ የሚያስፈልገውን በጀት በማዘጋጀት ያስፈቅዳል ተግባራዊነቱንም ይከታተላል ያረጋግጣል፤
የድርጅቱ የግቢ ጥበቃ አስተማማኝ መሆኑን ይከታተላል፣ ይቆጣጠራል፤
ለድርጅቱ ሠራተኞች የሚያስፈልጉ የቢሮ መገልገያ ዕቃዎች፣ መሣሪያዎችና ሌሎች አስፈላጊ ጉዳዮች በወቅቱ መሟላታቸውን ይከታተላል ይቆጣጠራል፤
በድርጅቱ ደንብና መመሪያ መሠረት ለሠራተኞች መስጠት የሚገባው የሥራ ላይ የአደጋ መከላከያ የሥራ ልብስና የመሳሰሉት በወቅቱ እንዲደርሳቸው ያደርጋል፡፡
በኢንሹራንስ ፖሊሲ መሠረት የድርጅቱ ንብረትና የድርጅቱ ሠራተኞች የመድን ዋስትና ማግኘታቸውን ይከታተላል፤ በየዘመኑ መታደሱን ያረጋግጣል፤
በንብረት ወይም በሰው ላይ አደጋ በደረሰ ጊዜ በተገቢው የመድን ዋስትና መሠረት የካሳ ጥያቄ /claim/ በማድረግ ተከታትሎ ያስፈጽማል፤
የተሽከርካሪዎች የሕይወት ታሪክ፣ የነዳጅና የቅባት ፍጆታ የጥገና ወጪን በተመለከተ አስፈላጊ መረጃዎች በሙሉ መሟላታቸውን ያረጋግጣል፤
ማንኛውም የድርጅቱ ንብረት ተገቢ ጥበቃና ጽዳት የተሟላ መሆኑን፣ የቢሮ መሣሪያዎች፣ ቋሚ ንብረቶች፣ ተሽከርካሪዎችና ሕንፃዎች አስፈላጊው ጥገናና ዕድሳት በሚያስፈልጋቸውና ከቅርብ አለቃው ሲፈቀድ በሚተላለፍለት መመሪያ መሠረት ጥገናዎቹ በወቅቱ እንዲከናወኑ በመከታተል ያስፈጽማል፤
የድርጅቱ ቢሮዎች ሕንፃ፣ ግቢና የመገልገያ መሣሪያዎች ወቅታዊ ጥገናና ዕድሳት እንዲደረግላቸው ይከታተላል፤
የእሳት አደጋ መከላከያዎች በየቦታው ተሟልተው እንዲቀመጡና በየአካባቢው ያሉ ሠራተኞችም በሙያው በቂ ስልጠና እንዲያገኙ ያደርጋል፤
ለጥበቃ፣ ለጽዳት ሠራተኞች፣ ለተላላኪዎችና ለሰርቪስ ሾፌሮች ወዘተ…….አስፈላጊውን የሥራ ፕሮግራም በማውጣት ይደለድላል አፈጻጸሙን ይቆጣጠራል፤
የስልክ፣ የመብራትና የውሃ መስመሮች አገልግሎት ሲያቋርጡ ከሚመለከታቸው መስሪያ ቤቶች ጋር በአስቸኳይ በመነጋገር አገልግሎታቸውን እንዲቀጥሉ ያደርጋል፤
የፎቶ ኮፒና የህትመት አገልግሎቶች በተሟላ ሁኔታ መስጠታቸውን ይከታተላል፣ ይቆጣጠራል፤
የስልክ አጠቃቀም፣ የመብራትና የውኃ አገልግሎት ፍጆታ በቁጠባ እንዲሆን ይከታተላል፣ ወርሃዊ የአገልግሎት ክፍያዎችን እየተከታተለ ያስፈጽማል፤
በአዲስ ወይም በነባር የሥራ መደቦች ላይ ሠራተኞች ለመመደብ አስፈላጊ ሆኖ በሚገኝበት ጊዜ በቅርብ ኃላፊው በሚሰጠው መመሪያ መሠረት ለተወዳዳሪዎች ማስታወቂያ ያወጣል፣ ተወዳዳሪዎችንም ማስረጃዎቻቸውን አረጋግጦ ይመዘግባል፤
የሠራተኞች የሥራ አፈጻጸም ምዘና ሪፖርት በወቅቱ ተሞልቶ በሠራተኞች የግል ማኅደር ውስጥ እንዲካተትና እንዲቀመጥ ያደርጋል፤
የሠራተኛ ቅጥር ወይም ዕድገትና ዝውውር እንዲሁም ጡረታና ስንብት በሚፈጸምበት ጊዜ አዋጅንና ኅብረት ስምምነቱን ተከትሎ አስፈላጊውን ይፈጽማል፤
የድርጅቱ የሥራ ሰዓትና የሥራ ዲሲፕሊን እንዲከበር ከሚመለከታቸው የሥራ ቅንጅት ይፈጥራል፣ የሠራተኞች የዲሲፕሊን ሁኔታ እንዲሻሻልና የሥራ ተነሳሽነት እንዲጎለብት አስፈላጊውን ሥልጠና ይሰጣል፤
የድርጅቱን የሥራ እንቅስቃሴ በማይጎዳ መንገድ ሠራተኞች የዓመት ዕረፍት ፈቃዳቸውን በወቅቱ እንዲወስዱ ከቅርብ ኃላፊው ጋር በመመካከር ፕሮግራም ያዘጋጃል፣ አፈጻጸሙን ይከታተላል፤
የሠራተኞች ደመወዝና የትራንስፖርት አበል በወቅቱ እንዲከፈል ከሰዓት ቁጥጥር ሰራተኛ የሚቀርብለትን መረጃ መሠረት በማድረግ በማጣራትና በማረጋገጥ ዝርዝሩን በወቅቱ ለሂሳብ የሥራ ዘርፍ እንዲተላለፍ ያደርጋል፤
የድርጅቱ ሠራተኞች የሚያቀርቡትን የሕክምና የተለያዩ የፈቃድ ማስረጃዎች ከአዋጁና ከድርጅቱ የአስተዳደር መመሪያ ጋር አመሳክሮና አረጋግጦ ለሚመለከታቸው የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ያስተላልፋል፤
በሠራተኞች የግል ማኅደሮች ውስጥ መያዝ የሚገባው መረጃዎችና ሰነዶች ተሟልተውና ሚስጥራቸው ተጠብቆ መያዛቸውን ያረጋግጣል፤
በሥሩ ለሚገኙ ሠራተኞች ሚዛናዊ የሆነ የሥራ ሥምሪት ይሰጣል የሥራ አፈጻጸማቸውን ይገመግማል ሪፖርት ያደርጋል፤
በተጨማሪም ሌሎ ከቅርብ ኃላፊው የሚሰጠውን ተመሳሳይ ሥራዎችን ያከናውናል፤
ከታወቀ ዩኒቨርስቲ/ ኮሌጅ ዲግሪ ወይም በቀድሞው የትምህርት ፖሊሲ 12+4 ወይም በአዲሱ የትምህርት ፖሊሲ 10+3 በሥራ አመራር፣ ሕዝብ አስተዳደር ወይም በተመሳሳይ የትምህርት መስክ የተመረቀ/ች
3 ዓመት የሥራ ልምድ ያለው/ላት
አመልካቾች የትምህርት፣ የሥራ ልምድ ደብዳቤ የማይመለስ ኮፒ ይዛችሁ በድርጅቱ ኢ-ሜይል: hrminaye@gmail.com ወይም ቃሊቲ ገብርኤል ኢንዱስተሪያል መንደር አካባቢ ዴሉክስ ፈርኒቸር ፋብሪካ በአካል በመቅረብ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናስታውቃለን። ለበለጠ መረጃ ስልክ 0114717381
Fields Of Study
Public Administration
TVET
Management
Related Jobs
2 days left
SHANGTEX GARMENT MANUFACTURING ETHIOPIA PLC
HR Manager
Human Resource Management Specialist
Full Time
2 - 5 yrs
1 Position
PhD, Master's or Bachelor's Degree in Human Resource Management or in a related field of study with relevant work experience Duties & Responsibilities: - Supervise and implement the company's existing HR management system, ensure that daily work is executed in an orderly manner and implemented in accordance with regulations, and maintain the company's authority. - Responsible for the recruitment of all local employees, complete the recruitment tasks within the specified time, and be responsible for the results. - Responsible for training local employees and tracking the results. The training includes but is not limited to company culture, factory disciplines, relevant laws and regulations, and customer compliance requirements. - Assist other departments to handle employee complaints and improve employee relations to ensure that daily work and production are not affected and there are no major strikes.
about 21 hours left
Diriba Defersha General Construction
Project Human Resource & Property Administration Head
Human Resource Management Specialist
Full Time
4 - 6 yrs
2 Positions
BA Degree or Diploma in Management, HRM or in a related field of study with relevant work experience Place of Work: Projects
about 21 hours left
Diriba Defersha General Construction
Personnel Officer
Personnel Officer
Full Time
2 - 3 yrs
3 Positions
BA Degree or Diploma in Management, HRM or in a related field of study with relevant work experience
2 days left
British Embassy in Ethiopia
HR Officer
Human Resource Officer
Full Time
3 yrs
1 Position
BA Degree in Human Resource Management, Business Management, Psychology or in a related field of study with relevant work experience Duties and Responsibilities: - Creates, maintains HR databases and information systems and periodically updates and generates employee data, various metrics, organograms, etc. - Uses analytical tools to ensure that there is up-to-date and consistent live data for all related HR functions. - Regularly conduct employee data analysis, e.g. descriptive statistics and other appropriate visualisation methods (e.g. dashboards, reports) and turn data into usable insights.
3 days left
Samanu Proudly Ethiopian
HR Officer
Human Resource Officer
Full Time
2 yrs
1 Position
Bachelor's Degree in Human Resources Management, Management or in a related field of study with relevant work experience Duties & Responsibilites: - Create a staff database and keep track of all relevant staff information. - Ensure job offer letters, contract agreements are timely prepared with Job description and signed by the employee. - Ensure that each employee has completed all pension formalities and has obtained a pension ID card. - Keep and update staff leave records.
3 days left
Zamra Construction P.L.C.
Senior HR Administration Officer
Human Resource Officer
Full Time
4 yrs
1 Position
BA in Human Resource Management, Business Administration, Management or in a related field of study with relevant work experience